Friday, April 27, 2012

ለእኛ ሰፈር ልጆች


ለእኛ ሰፈር ልጆች 
እኛ ልጅ ሆነን ያደግን 
በአፈር ተጫውተን ውሀ የተራጨን 
በፍቅር ተቃቅፈን ሲያሻን የተቧቀስን 
እኛ የድሮቹ
የጥንት ልጆቹ
በተጫወትንበት ባደግንበት ሜዳ
እኛ እንቆጥራለን እድሜያችን ሲቀዳ
"እርጅና መጣና ድቅን አለ ፊቴ"

ይሄን አንዘፍናለን ቀርቶ እቴሜቴ
እረ ቅሽምና ነው…….
ምንም ሳንሰራ አገር ሳናቀና አገር ሳንለውጥ
ወይ መንግስት ሣንቀይር ዝም ብለን ስንመርጥ
ወይ እንደነትና ካገር ሳንሰደድ
ዶላር ሳናመጣ
……………. እርጅናችን ይምጣ ¿¿¿¿¿
ወይ እንደነትና በእንትን ተይዘን እስር ቤት ሳንገባ
አልያም ጎጆ ብለን ሚስት ሳናገባ 
ወይ እንደነ ጒዴ ከጠረፍ ለማለፍ 
በምናምን አርገን በእንትን በኩል ስናለፍ
ህይወታችን ሳያለፍ
…… ወጣትነት ብቻ
ጥንካሬ ብቻ ከእኛ እያለፈ 
የእርጅናችን ሰነድ ከግንባር አረፈ
እኛ አኮ የምር ቀሽም ነን
ወይ እንደነእንትኖች አመጽ አስነስተን መንግስትን ሳንመርቅ
ወይ ከሀገር ተሰደን ለልማቱ ሳንጠደቅ
አልያም እነዳንዳንዶች ጋዜጣ ላይ መጻፍ መንግስትን ማማረር
ምንም በማናውቀው ጣልቃ እየገባን ዝምብለን መናገር
ይህ ሁሉ ያልሆነልን 
እርጅናችን ብቻ ጮቤ ሚረግጥብን 
ምን አይነት ጉዶች ነን
……… በቃ ክፈትልኝ የጒዴ ይሻላል 
"
እርጅና መጣና ድቅን አለ ፊቴ"
እባክህ ጨርሰው አንተ ሰው በሞቴ!!!!!!!!!!
10/07/04
E.T

No comments:

Post a Comment