ካለውበት ስፍራ የብረት ቅልጭታ እጅግ ከበዛበት
ግርግር ሁካታ ጎልቶ ከሞላበት
ይሰማኛል ዜማ የመቅደሱ ደውል
የካህኑን ፍታት ተከትሎ አሜን ሲል
ይሰማኛል ወገን በተመስጦ ሆኖ
ከደኙ ሲማጠን በፈጣሪው አምኖ
ይሰማኛል ከዚ ከጫጫታው መሀል
ተንስዑ የሚለው
ስገዱ የሚለው
የዲያቆኑ ቃጭል
ዲያቆኑ ለጥቋል
ወደ ምስራቅ እዩ ተመልከቱ ወደዛ
ይላል መሀል ቆሞ በእጣኑ መዓዛ
ከምዕራብ ያለው ከምስራቅ ርቄ
እኔ ከዚ ያለው ለዓለም ወድቄ
ዓለምን ናፍቄ
የምስራቁን ጥሪ የዲያቆኑን ዜማ
ለነፍስ የተስማማ
በናፈቀ ልቤ ባህር አሻግሬ
ተራራ አሳብሬ
የምስራቋን ሀገር ቅዳሴ አደምጣለው
የእጣን መዓዛን በማያውቅ አየር ውስጥ እጣን አሸታለው
ጉልበቴን በሀሳብ ከደጁ ሰድጄ ጌታ ሆይ እላለለው
እላለው እላለው እላለው እላለው።
ኤልያስ .ታ
07/22/2015
ግርግር ሁካታ ጎልቶ ከሞላበት
ይሰማኛል ዜማ የመቅደሱ ደውል
የካህኑን ፍታት ተከትሎ አሜን ሲል
ይሰማኛል ወገን በተመስጦ ሆኖ
ከደኙ ሲማጠን በፈጣሪው አምኖ
ይሰማኛል ከዚ ከጫጫታው መሀል
ተንስዑ የሚለው
ስገዱ የሚለው
የዲያቆኑ ቃጭል
ዲያቆኑ ለጥቋል
ወደ ምስራቅ እዩ ተመልከቱ ወደዛ
ይላል መሀል ቆሞ በእጣኑ መዓዛ
ከምዕራብ ያለው ከምስራቅ ርቄ
እኔ ከዚ ያለው ለዓለም ወድቄ
ዓለምን ናፍቄ
የምስራቁን ጥሪ የዲያቆኑን ዜማ
ለነፍስ የተስማማ
በናፈቀ ልቤ ባህር አሻግሬ
ተራራ አሳብሬ
የምስራቋን ሀገር ቅዳሴ አደምጣለው
የእጣን መዓዛን በማያውቅ አየር ውስጥ እጣን አሸታለው
ጉልበቴን በሀሳብ ከደጁ ሰድጄ ጌታ ሆይ እላለለው
እላለው እላለው እላለው እላለው።
ኤልያስ .ታ
07/22/2015

No comments:
Post a Comment