Wednesday, July 22, 2015

ተንስዑ

ካለውበት ስፍራ የብረት ቅልጭታ እጅግ ከበዛበት
ግርግር ሁካታ ጎልቶ ከሞላበት
ይሰማኛል ዜማ የመቅደሱ ደውል
የካህኑን ፍታት ተከትሎ አሜን ሲል
ይሰማኛል ወገን በተመስጦ ሆኖ
ከደኙ ሲማጠን በፈጣሪው አምኖ
ይሰማኛል ከዚ ከጫጫታው መሀል
ተንስዑ የሚለው
ስገዱ የሚለው
                     የዲያቆኑ ቃጭል
ዲያቆኑ ለጥቋል
ወደ ምስራቅ እዩ ተመልከቱ ወደዛ
ይላል መሀል ቆሞ በእጣኑ መዓዛ
ከምዕራብ ያለው ከምስራቅ ርቄ
እኔ ከዚ ያለው ለዓለም ወድቄ
                      ዓለምን ናፍቄ
የምስራቁን ጥሪ የዲያቆኑን ዜማ
                       ለነፍስ የተስማማ
በናፈቀ ልቤ ባህር አሻግሬ
                 ተራራ አሳብሬ
የምስራቋን ሀገር ቅዳሴ አደምጣለው
የእጣን መዓዛን በማያውቅ አየር ውስጥ እጣን አሸታለው
ጉልበቴን በሀሳብ ከደጁ ሰድጄ ጌታ ሆይ እላለለው
እላለው እላለው እላለው እላለው።

              ኤልያስ .ታ
               07/22/2015

No comments:

Post a Comment