Sunday, April 26, 2015

አቤቱ የሆነብኝን አስብ

አቤቱ የሆነብኝን አስብ

በጲላጦስ ፍርድ ላይ በሀሰት ስትወነጀል
ጀርባክ በጅራፍ ደምቶ ጉልበትክ በዳገት ሲዝል
አብራክ እንደደማችው በሀዘን ውስጧ ተሰብሮ
እንደ አዛኝቷ እናትክ ሀዘኗ ለሆነክ አብሮ
እነደሷ እኔም አነባው ልቤ በሀዘን ደማ
የምናገረው ላይኖረኝ ልጄ በሞት ተቀማ
… አቤቱ የሆነብኝን አስብ…
የሚፈስ ጣሪያዬን ሊደፍን ከእቅፌ እርቆ የሄደ
ምስኪኑ ያብራኬ ክፋይ በረሀ ገብቶ ወደቀ
ማተቡን እንዳጠበቀ…
… እጆችክ ከመስቀል ጋራ በምስማር ሲቸነከሩ
አካል በደም ተሞልቶ አጥንቶች ሲቆጠሩ
በእንባ የተሞላችው አንጀቷ ችሎ ያልቻለው
እናትክ ስንቱን አየችው
እኔም ምስኪኑ ልጄ እቅፌን ገና ያልጠገበው
አንገቱ በካራ ስለት ሲታረድ እንዴት ልቻለው
መሶቤን ሙሉ ሊያደርግ በረሀ ገብቶ የቀረ
ለኔ ሊያሳልፍ ሲጥር ባንገቱ ካራ አለፈ
እንዴት ልቻለው ከቶ የልጄን መታረድ ባይኔ
የደሙን መፈሰስ እያየው ጠፈብኝ የለቅሶ ወኔ
ልጄ ክብሬ ማረጌ የአይኔ ማረፊያ ሀብቴ
ስቅታው የሚያባንነኝ ተቀላ ይህው ከፊቴ
… አቤቱ የሆነብኝን አስብ …
ልጄ ስልጣን የለውም ሞትን ድል አርጎ አይመጣም
ዳግም ከእቅፌ ሆኖ እናቴ እነሆኝ አይልም
ታድያ ለዚ ምስኪን ደም ባህሩን ቀይ ላረገ
ሀሳቡን ከጫፍ ሳያደርስ በእንጭጩ ለጠወለገ
ምላሽክ አይዘግይ ጌታ ሆይ.. የፍርድህን ቀን አቅርብ
አቤቱ እለምናለው የሆነብኝን አስብ፡፡


 በሊቢያ በረሀ አርገው ወደ ፈጣሪያቸው ላቀኑ ሰማህታት።

                                                                              ኤ..ታ   04/22/2015

No comments:

Post a Comment